ከ1500 በላይ አማርኛ ተናጋሪዎች በኦሮሚያ ተጨፈጨፉ

 ethiopian human right commussion
22 June 2022

by Dawit Atreso

"ፈጣሪዬን ጠየኩት ለምን እኔን አተረፍከኝ ብዬ" ይህን ልብ የሚነካ ንግግር የተናገሩት 32 ቤተሰባቸውን በዘረኛው እና በ ብልፅግና ፓርቲ በቀጥታ በሚደገፈው በኦነግ ታጣቂ ጭፍጨፋ ያጡት ሰው ናቸው። በተለይም ይህ አማራን እና አማርኛ ተናጋሪ ጠልነት በይፋ ከ4 ዓመታት በፊት በግልፅ በጥላቻ እና በሀገሪቱ በይፋ ለተንሰራፋው ሁሉን አቀፍ ተረኝነት መታያ ሆኗል። በተለይም ዘረኛው አብይ አህመድ በቀጥታ ስርጭት በፓርላማው በይፋ የዘረኝነት ቅስቀሳ እና የጥላቻ ቅስቀሳ ንግግር በማድረግ ላይ ይገኛል።

ይህንንም ከሚያረጋግጡት ማስረጃዎች አንዱ ድግሞ ዘረኛው ጠቅላይ ሚንስትር በኦሮሚያ ክልል በምክትል ፕሬዝዳንትነት ሲራ የተናገረው አሁን ላይ አፍትልኮ በመውጣት ላይ ይገኛል። በዚያን ወቅት ከተናገረው ውስጥ የ ኦሮሞ ህዝብ መሬትን ለሌላው ብሄር መሸጥ እንደሌለበት እና የመሬትን ጉዳይ በተቻለ አቅም ችላ እንዳይሉት ሲያሳስብ ተደምጧል። ይህ ንግግር በስልጣን ላይ በወጣበት ወቅት ለኢትዮጵያ ህዝብ ቃል ከገባውና አንድነትን ከሰበከበት ጋር የተራራቀ ነው። በተለይም በዚህ ወቅት ኢትዮጵያ ለገባችበት ውጥንቅጥ በቀጥታ ተጠያቂ የሚሆነው አካል የኦሮሞው መንግስትና መሪው ናቸው።

ታድያ የጠቅላዩን ትእዛዝ በቀጥታ በመቀበል በ ወለጋ ጊምቢ በከፋ ሁኔታ ከ 1 ወር ህፃን እስከ 100 ዓመት አዛውንት በመንግስት ተቀጣሪ አነግ ታጣቂዎች በአሰቃቂ ሁኔታ ተጨፍጨፈዋል። በጭፍጨፋው ወቅት በስፍራው ከነበሩት እና ካመለጡት ሰው ያገኘነው መረጃ እንደሚያመለክተው በወቅቱ መከላከያ በወጣበት ቅስፈት ነው መተው ጭፍጨፋውን የጀመሩት ብለዋል። አክለውም ወዲያው የስልክ እና ኢንተርኔት አገልግሎት መቋረጡን ገልፀዋል።